top of page

የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚያጋጥማቸውን የፀጥታ እና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱ በመደረጉ የሚያመርቱ የምርት መጠን ጨምሯል ሲል የማዕድን ሚኒስቴር ተናግረ

  • sheger1021fm
  • May 30, 2024
  • 1 min read

የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚያጋጥማቸውን የፀጥታ እና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱ በመደረጉ የሚያመርቱ የምርት መጠን ጨምሯል ሲል የማዕድን ሚኒስቴር ተናግረ፡፡


የአገሪቱን የሲሚንቶ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳድገው የተነገረለት የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ግፋ ቢል በሁለት ወር ውስጥ ምርት እንደሚጀምር የማዕድን ሚኒስትሩ ሀብታሙ ተገኝ ለህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት አስረድተዋል፡፡


ምርት አቁሞ የነበረው የምሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ዳግም ስራ መጀመሩ እንዲሁም የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ችግር የሆነባቸው የፀጥታ ችግር እንዲፈታ በመሰራቱ የሲሚንቶ ምርት ጨምሯል ያሉት ሚኒስትር ሀብታሙ በዚህም ባለፉት 9 ወራት 5.4 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ ተመርቷል ብለዋል፡፡


ይህም የእቅዱን 85 በመቶ ነው፣ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የ22 ብልጫ አሳይቷል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ ይህንን ይጫኑ…


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page