ዘንድሮ በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 66 በመቶዎቹ ተማሪዎቻቸው ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡
- Jun 29
- 1 min read
ሰኔ 22/2018
ዘንድሮ በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 66 በመቶዎቹ ተማሪዎቻቸው ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡
የከተማዋ ትምህርት ቢሮ በሰጠው መግለጫ ከመንግስት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች 95 ነጥብ 8 በመቶ፤ ከግል ት/ቤት ተማሪዎች ደግሞ ከ99 በመቶ በላዩ ማለፋቸውን ተናግሯል፡፡
የማለፊያ ነጥቡ 50 በመቶና ከዚያ በላይ ሲሆን 1 ሺህ 313 ተማሪዎች ከ90 በመቶ በላይ አግኝተዋል፡፡
በትምህርት ቢሮ ማህበራዊ ትስስር ገፅ የተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ ተማሪዎች ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ......
ፋሲካ ሙሉወርቅ
_edited.jpg)




Comments