ወ/ሮ ሐይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ሹመት በህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት ፀደቀ።
- Jan 6
- 1 min read
ታህሳስ 28/2018
ወ/ሮ ሐይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ሹመት በህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት ፀደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሹመቱን ያጸደቀው 8ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ ባካሄደበት ወቅት ነው።

ዛሬ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን እንዲመሩ የተሾሙት ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ያለፈውን አንድ ዓመት ያህል ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር )ይተካሉ።
ሳምሶን መኮንን(ዶ/ር) በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው ተነግሯል።

ዛሬ ሹመታቸው የጸደቀላቸው ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ ከ20 ዓመታት በላይ በመገናኛ ብዙሃን እና ተያያዥ ሞያ ላይ የቆዩ መሆናቸው ተነግሯል።
አዲሷ ተሿሚ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በውጪ ቋንቋ እና ስነ ፁሁፍ እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ ከህንድ በሶሾዮሎጂ ተመርቀዋል ተብሏል።
ዛሬ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን እንዲመሩ የተሾሙት ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ፤ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሪፖርተር እና ኤዲተር በመሆን፣ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮፖሬሽን በተለያዩ የስራ ዘርፎች አገልግለዋል ሲባል ሰምተናል።
የዛሬው ሹመታቸው እሰኪጸድቅ ድረስ ደግሞ የአዲስ አበባ ስራ አስኪያጅ ቢሮ በምክትል ኃላፊ መዕረግ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ ነበር ተብሏል።
ያሬድ እንዳሻው





I found this update interesting and informative, especially regarding the recent leadership appointment and media authority changes. In my free time, I like to unwind with games, and Subway Surfers is one I keep coming back to because it's simple, fast-paced, and really relaxing to play for a few minutes.