top of page

እስራኤል በኢራን ላይ ድንገተኛ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ፡፡

  • Feb 28
  • 1 min read

የካቲት 21/2018

 

እስራኤል በኢራን ላይ ድንገተኛ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ፡፡

 

አልጀዚራን ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ጥቃቱን የተመለከተ መረጃን በሰበር ወሬ ይዘው ቀርበዋል፡፡



እስራኤል በፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በቴህራን ማዕከላዊ ከተማ የፍንዳታ ድምፅ መሰማቱ ተሰምቷል፡፡

 

ፋርስ የወሬ ምንጭ እንደዘገበው በማዕከላዊ ቴህራን ዩኒቨርስቲ ጎዳና እና ጃዋሆሪ በተባሉት ማዕከላዊ የቴህራን ክፍል ተደጋጋሚ የሚሳኤል ጥቃት ተሰንዝሯል፡፡

 

የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እርምጃው እራስን ከጥቃት የመጠበቅና ቀርቦ የመከላከል ነው ብለውታል፡፡

 

አሶሼትድ ፕሬስ የመረጃ ምንጭ ደግሞ የእስራኤል ጥቃት የተፈፀመው በኢራን ዋና ከተማ በከፍተኛ መንፈሳዊው መሪው አያቶ አሊ ካሚኒ ቢሮ አካባቢ ነው ብሏል፡፡

 

ዝርዝር መረጃ ግን እስካሁን አልወጣም፡፡

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page