top of page

ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ያላቸው ድርሻ ከ5 እስከ 7 በመቶ ነው ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • 7 days ago
  • 1 min read

ጥር 26/2018


ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ያላቸው ድርሻ ከ5 እስከ 7 በመቶ ነው ተባለ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በጎረቤት ሀገራት ባንኮች ለሀገራቸው ጠቅላላ ኢኮኖሚ ያላቸው ድርሻ ከዚህ ይበልጣል ለዚህም ምንክያቱ ባንኮቹ አቅማቸው ስለደረጀና የውጪ ባንኮች ስለገቡ ነው ብለዋል፡፡


ባለፉት 30 ዓመታት የኢትዮጵያ ባንኮች ያለውም ውድድር እንዲሰሩ ቢደረግም የታሰበውን ያህል ሀብት መፍጠር አልቻሉም ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮችም አቅማቸው ማደርጀት አለባቸው ያሉ ሲሆን የውጪ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባት አለባቸው ብለዋል፡፡


ከውጪ የሚመጡ ባንኮች አጠቃላይ መያዝ የሚችሉት 49 በመቶ ድርሻ ብቻ ነው 5 ለውጪ ባንኮች የሚሠጥ ፍቃድ በ5 አመት ውስጥ የሚካሄድ ነው ሲሉም አስረድተዋል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ባንኮች ባንክ መሆን አለባቸው በየሰፈሩ መከፈት የለባቸውም ጠንካራ ባንክ ለመሆን የሚያስችል አቅም አላቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ የባንኮች ቁጥር ከ5 እስከ 10 በቂ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page