top of page

ሐምሌ 30፣2016 - ኢትዮጵያ ወደ ውጭ የምትልከውን የቡና ምርት በብዙ እጥፍ ሊያሳድጉ የሚችሉ የቡና ዝርያዎች በምርምር ተገኙ

  • sheger1021fm
  • Aug 6, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ የምትልከውን የቡና ምርት በብዙ እጥፍ ሊያሳድጉ የሚችሉ የቡና ዝርያዎች በምርምር ተገኙ፡፡


ሀገሪቱ በ1 ሄክታር ከምታገኘው የቡና ምርት ከ3 እጥፍ የሚበልጡ የቡና ዝርያዎች በምርምር ተገኝተዋል፡፡


ዝርያዎቹ ለፍሬ ሲበቁ አሁን ከአንድ ሄክታር የሚገኘውን 7 ኩንታል ወደ 23 ኩንታል እንደሚያሳድጉትም ሰምተናል፡፡


በጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር የተገኙት ዝርያዎች 5 ሲሆኑ 3ቱ ለቆላማ አካባቢዎች፣ 2ቱ ደግሞ ለደጋማ አካባቢዎች የአየር ንብረት የተመቹ መሆናቸውን የማዕከሉ ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ግርማ ሃይለ ሚካኤል ነግረውናል፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page