የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ከስልጣን በማንሳት አዲስ ርዕሰ መስተዳድር ፕሬዚዳንት ሾመ፡፡
በምትካቸውም ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በመሆን ተሹመዋል፡፡
የአመራር ለውጥ ያስፈለገበት ምክንያት በክልሉ በሠላምና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ዘርፍ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም የተቀመጡ አቅጣጫዎች ውስንነቶች በመታየታቸው ነው ተብሏል፡፡
በተጨማሪም ከስድስት ዓመት በላይ ክልሉን ሲመሩ የቆዩት የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ለሌላ የፓርቲ ተልዕኮ በመፈለጋቸው መሆኑ ተነግሯል።
በምክር ቤቱ የተሾሙት ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ቀደም ሲል በጋምቤላ ክልል የሴቶችና ህፃናት ቢሮ በኃላፊነት እንዲሁም በሌሎች ቢሮዎች በኃላፊነት አገልግለዋል።
ወደዛሬው ሹመት እስከመጡበት ድረስም በኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ሲያገለግሉ ነበር ሲል ክልሉ ተናግሯል።
የክልሉ ምክር ቤት በዛሬው አስቸኳይ ጉባኤው አዲስ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርም ሹመት አጽድቋል፡፡
በዚህም ጋትሏክ ሮን(ዶ/ር) የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መርጧል።
ጋትሏክ ሮን(ዶ/ር) በኢፌዴሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ሆነው እያገለገሉ እንደነበር ክልሉ በማህበራዊ የተስስር ገጹ ላይ አስፍሯል።
ማንያዘዋል ጌታሁን
Comments