top of page

ነሐሴ 9፣2016 - ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በመሆን ተሾሙ፡፡

  • sheger1021fm
  • Aug 15, 2024
  • 1 min read

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ምክር ቤቱ ሹመቱን ያፀደቀው ዛሬ ባካሄደው 6ኛ የምርጫ ጊዜ 3ኛ የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው።


የአመራር ለውጥ ያስፈለገበት ምክንያት በክልሉ በሠላምና ፀጥታ እንዲሁም በልማት ዘርፍ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም የተቀመጡ አቅጣጫዎች ውስንነቶች በመታየታቸው ነው ተብሏል፡፡

በተጨማሪም ከስድስት ዓመት በላይ ክልሉን ሲመሩ የቆዩት የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ለሌላ የፓርቲ ተልዕኮ በመፈለጋቸው መሆኑ ተነግሯል።


በምክር ቤቱ የተሾሙት ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ቀደም ሲል በጋምቤላ ክልል የሴቶችና ህፃናት ቢሮ በኃላፊነት እንዲሁም በሌሎች ቢሮዎች በኃላፊነት አገልግለዋል።


ወደዛሬው ሹመት እስከመጡበት ድረስም በኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህፃናት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ሲያገለግሉ ነበር ሲል ክልሉ ተናግሯል።


ማንያዘዋል ጌታሁን

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page