top of page

ነሐሴ 7፣2016 - የኢንቨስትመንት ቢሮ የግል ትምህርት ቤቶችን ለመደገደፍ የህግ ማሻሻያ ባደርግም ብዙዎች እየተጠቀሙበት አይደለም ብሏል

  • sheger1021fm
  • Aug 13, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ቢሮ የግል ትምህርት ቤቶችን ለመደገደፍ የህግ ማሻሻያ ባደርግም ብዙዎች እየተጠቀሙበት አይደለም ብሏል፡፡


ሊጠናቀቅ አንድ ወር በቀረው 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ፍቃድ ወስደው ወደ ስራ የገቡ የግል ትምህርት ቤቶች ቁጥር 23 ናቸው፡፡


ነገር ግን ከነዚህ ውስጥ በቢሮው የሚሰጠውን ድጋፍ የወሰዱት ሁለት ብቻ መሆናቸውን ሰምተናል፡፡

ይህንን የሰማነው ከአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ቢሮ ነው፡፡


የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ቢሮ ከዚህ ቀደም የግል ትምህርት ቤቶችን አስተዳድርበት የነበረው አዋጅ ክፍተት ስለነበረበት እሱ ተሻሽሎ ወደ ስራ ከገባ በኋላ ግን የሚነሱት ችግሮች እየተፈቱ ነው ይላል፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page