top of page

ነሐሴ 6፣2016 - ‘’ምንዛሪ ገበያ መር አንዲሆን ለመወሰን ከዚህ የተሻለ ጊዜ የለም’’ በዓለም አቀፍ የእድገት ማዕከል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢኮኖሚስት ቴዎድሮስ መኮንን (ዶ/ር)

  • sheger1021fm
  • Aug 12, 2024
  • 1 min read

‘’የውጭ ምንዛሪ ገበያ መር አንዲሆን ለመወሰን ለኔ ከዚህ የተሻለ ጊዜ የለም’’ ሲሉ በዓለም አቀፍ የእድገት ማዕከል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢኮኖሚስት የሆኑት ቴዎድሮስ መኮንን (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡


የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ እንዲመራ ከወሰነበት እለት ጀምሮ ውሳኔው ልክ ነው ልክ አይደለም በሚል ባለሞያዎችን ለሁለት ከፍሎ እያሟገተ ነው፡፡


ከፊሎቹ ውሳኔው ወቅቱን ያልጠበቀ በገበያ ላይም ከፍተኛ ቀውስ የሚፈጥር ነው ሲሉ ገሚሶቹ ደግሞ ኢትዮጵያ ዘግይታም ቢሆን የማይቀርላትን ማሻሽያ አሁን ማድረጉ ተገቢ ነው የሚል ክርክር ያቀርባሉ፡፡


ባለፈው ቅዳሜ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ(ኢዜማ) ይህን የተመለከተ ወይይት አካሂዷል፡፡


በወይይት ላይ የተጋበዙት በአለም አቀፍ የእድገት መዕከል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢኮኖሚስት የሆኑት ቴዎድሮስ መኮንን(ዶ/ር) ማሻሽያውን ለማድረግ ከዚህ የተሻለ ጊዜ ለኔ የለም ይላሉ; ምክንያታቸውንም አስረድተዋል፡፡



ያሬድ እንዳሻው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page