top of page

ነሐሴ 3፣2016የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎችን ለመክፈት የስራ ፈቃድ ማመልከቻዎችን መቀበል እንደጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተናገረ።

  • sheger1021fm
  • Aug 9, 2024
  • 1 min read

የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎችን ለመክፈት የስራ ፈቃድ ማመልከቻዎችን መቀበል እንደጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተናገረ።


ማዕከላዊ ባንኩ ዛሬ ይፋ ባደረገው መረጃ ከሐምሌ 22 ጀምሮ ስራ ላይ በዋለው የውጭ ምንዛሬ መሰረት የውጭ ምንዛሬ መስራት የምትፈልጉ ማመልከቻ ማስገባት ትችላላችሁ ብሏል።


የውጭ ምንዛሬ ቢሮ ለመክፈት መስፈርቱን አሟልተው የሚገኙ፤ የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸው፣ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የሚኖሩ እንዲሁም የሌላ ሀገር ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን ማመልከት ይችላሉ ተብሏል።


የግል የውጭ ምንዛሮ ቢሮዎች እንዲከፈቱ የስራ ፈቃድ መሰጠቱ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ለመክፈት እና ዘርፉን በቀጣይ አመታት ተወዳዳሪ ለማድረግ ጠቃሚ መሆኑን  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ሞማ ምህረቱ ተናገረዋል።


ማንያዘዋል ጌታሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page