top of page

ነሐሴ 29፣2016 - ''አካል ጉዳተኞች በፖለቲካው እንዲሳተፉ መጠየቅን ጨምሮ ዋና ዋና ያልኳቸውን ሶስት አጀንዳዎች ለምክክር ኮሚሽን አስረክቢያለሁ'' የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን

  • sheger1021fm
  • Sep 4, 2024
  • 1 min read

''አካል ጉዳተኞች በፖለቲካው እንዲሳተፉ መጠየቅን ጨምሮ ዋና ዋና ያልኳቸውን ሶስት አጀንዳዎች ለምክክር ኮሚሽን አስረክቢያለሁ'' ሲል የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡


ፌዴሬሽኑ ውስብስብ ያልተፈቱ ችግሮች ያሉብን እኛ ስለሆንን አስቀድመን የለየናቸውን አጀንዳዎችን ለኮሚሽኑ እንዲመከርባቸው እና መፍትሄ እንዲገኙ አስረክቢያለሁ ሲል ተናግሯል፡፡


ከህግ መንግስት ጀምሮ ፖሊሲዎች ፤ህጎች ፤አዋጆች አካል ጉዳተኛን ታሳቢ ያደረጉ እሱን ያካተቱ እንዲሆኑ የሚጠይቀው አንደኛው አጀንዳ እንደሆነ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ ንግረውናል፡፡


ሁለተኛው ደግሞ አካል ጉዳተኞች በፖለቲካው እንዲሳተፉ ውሳኔ ሰጪ ቦታዎች ላይ እንዲቀመጡ የሚጠይቅ እንደሆነ ተነግሯል፡፡


በዚህም ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጋ ቁጥር ያለው አካል ጉዳተኛው በፖለቲካው ሊሳተፍ ይገባል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡


የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ የሚመራ ራሱን የቻለ ተቋም እንዲኖር የሚጠይቀው ደግሞ ሶስተኛ አጀንዳ ሆኖ ለምክክር ኮሚሽን ቀርቧል ሲል ፌደሬሽኑ ተናግሯል፡፡



ያሬድ እንዳሻው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page