top of page

ነሐሴ 28፣2016 - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ አስመራ የሚያደርገውን በረራ እንዳቋረጠ ተናገረ

  • Sep 3, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ አስመራ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያቋርጥ ተናገረ።


አየር መንገዱ ከነሐሴ 28፣2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያቋርጥ የተናገረው አመሻሹን ባወጣው መጎለጫ ነው።


በረራው የሚቋረጠውም ከአቅሙ በላይ በሆነ አስቸጋሪ የስራ ሁኔታ ምክንያት መሆኑንም አስረድቷል።


በዚህም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመብረር ትኬት የቆረጡ መንገደኞች  ያለምንም ተጨማሪ ወጪ በሌሎች አየር መንገዶች ጉዟቸውን እንዲያደርጉ ጥረት እንደሚያደርግሞ ጠቅሷል።

የትኬት ገንዘባችን ይመለስ የሚሉ ካሉም ለቲኬታቸው ሙሉ ገንዘብ ተመላሽ እንደሚያደረግ አስታውሷል።


በበረራው መቋረጥ ምክንያት  ለሚፈጠረው መጉላላት  ይቅርታ እንይቃለሁ ያለው አየር መንገዱ  ስለሚረዱትም አመስግኗል።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመስከረም 20፣2017 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ መብረር አንደማይችል ከኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በደብዳቤ አንደተናገረው መናገሩ ይታወሳል።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ማብራሪያ እየፈለገ መሆኑን ተናግሮ  ማንኛውንም ችግር በሰላማዊ መንገድ እና በፍጥነት ለመፍታት ቁርጠኛ ነኝ ሲል ሐምሌ 17፣2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።


የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኞች ከመስከረም 20፣2017 ጀምሮ ወደ ኤርትራ የሚደርጉትን በረራ አንደሚያግድ የተናገረው የተጓዦች ሻንጣ ይሰረቃል፣ተደጋጋሚ የበረራዎች እና የሻንጣዎች መዘግየት ያገጥማል በሚል ምክንያት አንደሆነ ተዘግቧል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page