top of page

ነሐሴ 28፣2016 የተፈጥሮ አደጋዎች በሚደርሱበት ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች ችግር ፈቺ ለመሆን ቀዳሚ መሆን አለባቸው ሲሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡

  • sheger1021fm
  • Sep 3, 2024
  • 1 min read

የተፈጥሮ አደጋዎች በሚደርሱበት ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች ችግር ፈቺ ለመሆን ቀዳሚ መሆን አለባቸው ሲሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡


በኢትዮጵያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ግን ይህንን ሲያደርጉ አይታይም ብለዋል፡፡


በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ችግር ፈቺዎች አደሉም ይላሉ፡፡


ይህ እንዲሆን ካደረጉት መካከል ደግሞ ዩኒቨርስቲዎች በመንግስት በጀት ስለሚንቀሳቀሱ ነው መባሉንም ሰምተናል፡፡

የሚያስጠኑት ጥናት የተማሪዎች የመመረቂያ ጹሁፍ ከወረቀት አልፎ ስራ ላይ ሲውል አይታይም የሚሉት ባለሞያው ዩኒቨርስቲዎች በራሳቸው በጀት የሚንቀሳቀሱ ቢሆን ኖሮ ለገቢያቸው ሲሉ ተግባር ላይ የሚውል ጥናት እና ምርምር ያደርጉ ነበር ብለዋል፡፡


ጥናቶች ሲደረጉ ቀድሞ የሚሆነውን ማረጋገጥ እና አንድ ችግር ከደረሰም በኃላ መፍትሄ ይዞ መምጣት እንዳለባቸው ተነግሮዋል፡፡


ማርታ በቀለ

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page