top of page

ነሐሴ 25፣2016 - ''ባለፈው አንድ ወር ብቻ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በህግ ጥሰት እርምጃም ወደ 25 ሚሊዮን ብር ሰብስቤአለሁ'' ደንብ ማስከበር ባለስልጣን

  • sheger1021fm
  • Aug 31, 2024
  • 1 min read

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ደንብ ተላልፈው የተገኙ ተቋማትና ግለሰቦች ላይ በተወሰደ እርምጃ ከ66 ሚሊዮን ብር በላይ የቅጣት ገቢ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ተናገረ፡፡


ባለስልጣኑ ባለፈው አንድ ወር ብቻ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በህግ ጥሰት እርምጃም ወደ 25 ሚሊዮን ብር ሰብስቤአለሁ ብሏል፡፡


ከደንብ ተላላፊዎች የተገኘው ገንዘብም ለፋይናንስ አስተዳደር ገቢ ሆኖ መልሶ ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል ይደረጋልም ተብሏል፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ ከ3 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ መፍጠሩንም ባለስልጣኑ ተናግሯል፡፡


ህገወጥ ንግድን ከመቆጣጠር እና የተለያዩ የደንብ ጥሰቶችን ከመከላከል አኳያ ትልቅ መሻሻሎች መጥተዋል ተብሏል፡፡


ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ባከናወነው ስራም የመሰረተ ልማቶች ውድመት እና ብልሽት እየቀሰነ መምጣቱም ተጠቅሷል፡፡


ፍቅሩ አምባቸው


Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page