top of page

ነሐሴ 24፣2016 - በጠለምት ወረዳ በደረሰው የመሬት መንሸራተት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ምንም ዓይነት የአስቸኳይ የእለት ድጋፍ አላገኙም ተባለ

  • sheger1021fm
  • Aug 30, 2024
  • 1 min read

በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በአብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኞላ በተባለ ቦታ በደረሰው የመሬት መንሸራተት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች እስካሁን ምንም ዓይነት የአስቸኳይ የእለት ድጋፍ አላገኙም ተባለ።


በመሬት መንሸራተት ሳቢያ የተፈናቀሉ የቤተሰብ አባላት ቁጥር 2,400 መሆናቸውንም ሰምተናል።

የጠለምት ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ወርቅነህ ‘’በወረዳው በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የአካባቢውን ነዋሪዎች ወደ ሌላ ቀዬ እንዲሰፍሩ ቢደረግም አደጋው ከተከሰተበት ነሀሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ምንም ዓይነት ድጋፍ አላገኙም’’ ብለዋል።


አቶ ተስፋዬ አያይዘውም በአካባቢው ባለው የፀጥታ ችግር ፣የመንገድ ፣ የኔትወርክ ፣ የባንክ እና መሰል የመሰረተ ልማት ችግር በመንግስት በኩልም ሆነ ከተለያዩ እረጅ ድርጅቶች ድጋፍ ለማግኘት መቸገራቸውን ለሸገር ተናግረዋል።


ፍቅሩ አምባቸው

Yorumlar


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page