top of page

ነሐሴ 24፣2016 - በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ የመንግስት መ/ቤቶች ንብረት ያላግባብ በሀላፊዎች እጅ እንደሚገኝ ኦዲት አረጋገጠ

  • sheger1021fm
  • Aug 30, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ የመንግስት መ/ቤቶች ንብረት ያላግባብ በሀላፊዎች እጅ እንደሚገኝ ኦዲት አረጋገጠ፡፡


የኦዲት ምርመራው 13 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት በሀላፊዎች እጅ እንደሚገኝ አሳይቷል፡፡


በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 269 ተቋማት ላይ በተደረገ የንብረት ቆጠራ ወደ 24 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት በጉድለት መገኘትንም ሰምተናል።


ጉድለት የተገኘባቸው የተቋማት ሃላፊዎች ላይም እርምጃ እንደተወሰደባቸውም ተነግሯል።


የአዲስ አበባ ከተማ #የመንግስት_ንብረት_አስተዳደር_ባለስልጣን የህንፃና ንብረት ኦዲት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ምሩጽ ታዬ፤ በተቋማቶች ላይ ከተገኘው ጉድለት ውስጥ ወደ 10.9 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት እንዲመለስ ተደርጓል ብለዋል።


አቶ ምሩፅ አያይዘውም በተቋማቱ ከተመዘገበው ንብረት ላይ ጉድለት የተገኘባቸው ሃላፊዎች ከስራ ገበታ እንዲባረሩ እና በህግ እንዲጠየቁ ተደርጓል ሲሉ ነግረውናል።



ፍቅሩ አምባቸው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page