top of page

ነሐሴ 23፣2016 - የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ102,000 ብር በላይ ተሸጠ

  • sheger1021fm
  • Aug 29, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ102,000 ብር በላይ ተሸጠ።


ይህም በታሪክ ከፍተኛ መሆኑ ተነግሯል።


በአራተኛው የባለልዩ ጣዕም ቡና ውድድር (ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ) ዓለም አቀፍ ጨረታ የኢትዮጵያ አንድ ኪሎ ቡና በ980 ዶላር ወይም ከ102,000 ብር በላይ መሸጡን እና አዲስ ክብረ ወሰን መመዘገቡን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስረድቷል።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ በቡና ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች የልፋታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል የባለ ልዩ ጣዕም ቡና ውድድር ከተጀመረ አምስት ዓመት ማስቆጠሩን ጠቅሰዋል።


አራተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ውድድር በተለያዩ የውድድር መርሃ ግብሮች ላለፉት ሰባት ወራት ሲካሄድ መቆየቱን ተነግሯል።


በዘንድሮው የውድድሩ ዓለም አቀፍ የኦንላይን ጨረታ ሂደት ተወዳዳሪ ለሆኑት ቡናዎች 4,870 የተለያዩ ዋጋ መሰጠቱንና ለአንድ ኪሎ ቡና የቀረበው የጨረታ ዋጋ ታሪካዊ ሆኖ መመዝገቡን ጠቁመዋል።


ውድድሩን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ከፍተኛ ጥረት ላደረጉ ተቋማት፣ አርሶ አደሮች፣ በቡናው ዘርፍ የተሰማሩና አጋሮች ዳይሬክተሩ ምስጋና አቅርበዋል።


አምስተኛው የባለልዩ ጣዕም ቡና ውድድር(ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ) በ2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።


ንጋቱ ሙሉ

Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page