top of page

ነሐሴ 22፣2016 - ለ24,000 የቴክኒክና ሞያ አሰልጣኝ መምህራን ስልጠና መስጠት ዛሬ ተጀምሯል

  • sheger1021fm
  • Aug 28, 2024
  • 1 min read

በዘርፉ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂዎችና አዳዲስ እሳቤዎች ላይ የአሰልጣኞችን ግንዛቤ ለማሳደግ ይረዳል የተባለ ስልጠና ለ24,000 የቴክኒክና ሞያ አሰልጣኝ መምህራን ስልጠና መስጠት ዛሬ ተጀምሯል፡፡


ስልጠናው ከዛሬ ነሃሴ 22 አስከ ጳጉሜ 3 የሚቆይ ሲሆን ‘’ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት’’ በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚሰጥ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡


በዚህም በ17 የስልጠና ማዕከላት 24,000 የሚጠጉ የቴክኒክና ሞያ አሰልጣኞች ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 12 ቀናት የሚካሄድ ይሆናል፡፡


‘’ይህ ስልጠና ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ ከቴክኒክ እና ሞያ የሚወጡ ተማሪዎችም ብቁ እና ወቅቱን የሚመጥን ክህሎት ኖሯቸው እንዲወጡ ይረዳል’’ ሲሉ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚል ተናግረዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page