top of page

ነሐሴ 20፣2016 - ከአሜሪካ የመጡ ከ17 በላይ የልብ ህክምና ባለሞያዎች ነፃ የልብ ህክምና መስጠት ጀመሩ

  • sheger1021fm
  • Aug 26, 2024
  • 1 min read

ከአሜሪካ የመጡ ከ17 በላይ የልብ ህክምና ባለሞያዎች ነፃ የልብ ህክምና መስጠት ጀመሩ፡፡


ለሁለት ሳምንት የሚቆየው የህክምና ቡድኑ 70 የልብ ህሙማን ያክማል ተብሏል፡፡


‘’ኸርት አታክ ኢትዮጵያ’’ የተሰኘው  ግብረ ሰናይ ድርጅት መቀመጫው በአሜሪካ ጆርጅያ እንደሆነና ከዚህ ቀደምም ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ለ32 ህሙማን የቀዶ ህክምና ማድረጉን ተናግሯል፡፡

በአሁኑ ደግሞ ለ43 ህሙማን  የቀዶ ህክምና ማድረጉ እና ለሁለት ሳምንት በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ማዕከል አገልግሎት እንደሚሰጥ ሰምተናል፡፡


ከዚህ በተጨማሪ ቡድኑ 1.3 ሚሊዮን  ዶላር የተገመተ ለህክምና የሚያገለግል መሳሪያ ይዞ መምጣቱን የኸርት አታክ ኢትዮጵያ መስራች መካከል አንዱ የሆኑት ተስፋዬ ተሊላ(ዶ/ር) ነግረውናል፡፡


‘’ከዚህ ቀደም ለበጎ አድራጎት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት ነጮች ብቻ ናቸው አሁን ግን ትውልደ ኢትዮጵያውያን በመሆናቸው እጅግ ደስ ብሎናል’’ ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል ስራ አስፈጻሚ አቶ ህሩይ አሊ ናቸው፡፡



ማርታ በቀለ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page