top of page

ነሐሴ 18፣2016 - ባለፉት 6 ዓመታት 40 ቢሊዮን ችግኝ ተተክሏል ተባለ

ባለፉት 6 ዓመታት 40 ቢሊዮን ችግኝ ተተክሏል ተባለ፡፡


በ2011 በተጀመረው ችግኝ የመትከል እቅድ 40 ቢሊዮን ችግኝ መተከላቸው ተነግሯል፡፡


ከተተከሉት 40 ቢሊዮን ችግኞች ውስጥ ለውበት፣ ለደን ለምግብና ለመኖ የሚያገለግሉ እንደሆኑ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል፡፡


በተናንትናው እለትም 600 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ 615.7 ሚሊዮን ችግኝ መትከል እንደተቻለ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስረድተዋል።


29.1 ሚሊዮን ዜጎች በ318.4 ሄክታር በጂኦስፓሻል መረጃ በተገኘባቸው ስፍራዎች ላይ ችግኞችን ተክለዋል ተብሏል።


እስካሁን በመረጃ ቋት ከተመዘገበው ውጭ የተተከሉ ችግኞች መረጃ በተከታታይ ይነገራል ተብሏል።


ለመሆኑ ሀገሪቱ በየዓመቱ የምትተክላቸው ችግኞች እየጠጸደቁ ነው ወይ፤ ምንስ ለውጥ አመጡ?


ምንታምር ጸጋው



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page