top of page

ነሐሴ 14፣2016 - የተደረገው ማሻሻያ ኤክስፖርቱን ዘርፍ ሊያበረታታው እንደሚችል ተነግሯል

  • sheger1021fm
  • Aug 20, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ ቡናዋንም፣ ወርቁንም፣ ጫቷንም ለውጭ ገበያ አቅርባ የምታገኘው ገቢ የነዳጅ ወጪዋን እንኳን አልሸፈነም፡፡


በአንፃሩ ሀገሪቱ ለገቢ ምርቶች ከ14 ቢሊዮን ዶላር በላይ ታወጣለች፡፡


በቅርቡ የተደረገው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ይህንን ከፍተት ያስተካክለዋል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል፡፡


ከዚህ ቀደም የነበረው ነጋዴውን በከፍተኛ ጫናውስጥ የከተተ ነበር፡፡


ይህ የተደረገው ማሻሻያ ኤክስፖርቱን ዘርፍ ሊያበረታታው እንደሚችል ተነግሯል፡፡


ነጋዴው ማህበረሰብ የተደረገውን ማሻሻያ በበጎ ጎኑ እንደተመለከተ የአዲስ ቻምበር ፕሬዝዳንት የሆኑት ወይዘሮ መሰንበት ሽንቁጤ ነግረውናል፡፡


በለውጡ የሚያንገራግጩ ነገሮች ቢኖሩም ከሌሎች ሀገሮች ልምድ መውሰድ ያስፈልጋልም ብለዋል፡፡


ነጋዴው ግራ እንዳይጋባ ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ፕሬዝዳንቷ አስረድተዋል፡፡



ማርታ በቀለ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page