top of page

ነሐሴ 13፣2016 - የተለያዩ የገቢ እቃዎች በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ መንግስት ያሳለፈው ውሳኔ ከዛሬ ጀምሮ ስራ ላይ ይውላል ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • Aug 19, 2024
  • 1 min read


የገንዘብ ሚኒስቴር ለጉምሩክ ኮሚሽን ዛሬ በላከው ደብዳቤ የተለያዩ ምርቶች ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ ወይም በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር እንዲገቡ የተላለፈውን ውሳኔ ስራ ላይ እንዲያውል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

መንግስት የውጭ ምንዛሪ በገበያው እንዲመራ መወሰኑን ተከትሎ የገቢ ንግዱን ለማቀላጠፍ ያስችል ዘንድ ውሳኔው እገዛ ያደርጋል ተብሏል፡፡


ከደብዳቤው እንደተመለከትነው እንዳይገቡ ከተከለከሉ ማለትም ከፀጥታ የደህንነት እቃዎች እንዲሁም ከነዳጅ አውቶሞቢሎች ውጭ ሌሎች ምርቶችን ያለ ውጭ ምንዛሪ ክፍያ ወደ አገር ማስገባት ይቻላል ተብሏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page