የገንዘብ ሚኒስቴር ለጉምሩክ ኮሚሽን ዛሬ በላከው ደብዳቤ የተለያዩ ምርቶች ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ ወይም በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር እንዲገቡ የተላለፈውን ውሳኔ ስራ ላይ እንዲያውል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
መንግስት የውጭ ምንዛሪ በገበያው እንዲመራ መወሰኑን ተከትሎ የገቢ ንግዱን ለማቀላጠፍ ያስችል ዘንድ ውሳኔው እገዛ ያደርጋል ተብሏል፡፡
ከደብዳቤው እንደተመለከትነው እንዳይገቡ ከተከለከሉ ማለትም ከፀጥታ የደህንነት እቃዎች እንዲሁም ከነዳጅ አውቶሞቢሎች ውጭ ሌሎች ምርቶችን ያለ ውጭ ምንዛሪ ክፍያ ወደ አገር ማስገባት ይቻላል ተብሏል፡፡
Comments