top of page

ነሐሴ 13፣2016 - ''በኤርትራ ሰራዊት በተያዙ አካባቢዎች ነዋሪዎች ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው'' እንባ ጠባቂ ተቋም የመቀሌ ቅርንጫፍjust now

  • sheger1021fm
  • Aug 19, 2024
  • 1 min read

‘’ዛላንበሳ ጨምሮ በኤርትራ ሰራዊት በተያዙ የኢሮብ አካባቢዎች ነዋሪዎች ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው’’ ሲል የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የመቀሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ተናገረ፡፡


በዛላንበሳን ጨምሮ በኤርትራ ሰራዊት እጅ በሆኑ የኢሮብ አካባቢዎች አገልግሎት መስጠት እንዳልቻለ ጽሕፈት ቤቱ አስረድቷል፡፡


‘’የፌደራል መንግስት እና በሃወሃት መካከል ተደርጎ በነበረው ጦርነት ምክንያት በኤርትራ ሰራዊት እጅ የገቡ አካባቢዎች ባለመለቀቃቸው የአካባቢው ተወላጆች ላይ ችግር እየደረሳባቸው’’ እንዳለ የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ ፀሃዬ እንባዬ ነግረውናል፡፡


በኢሮብ የነበረው የባንክ፣ የስልክ እና መሰል አገልግሎት በጦርነቱ ወቅት ከተቋረጠ ወዲህ ዳግም አልተመለሰም ተብሏል፡፡


በዚህም ምክንያት ‘’በኤርትራ ሰራዊት እጅ ባሉ እና ከኢሮብ አካባቢ ወደ አዲግራት እንዲሁም ጎረቤት ከተሞች 100 ኪ.ሜ ለማይሞላ መንገድ 600 ብር እየከፈሉ’’ እንደሆነ ኃላፊው ነግረውናል፡፡


በተያዙ አካባቢዎች ያሉ ትምህርት ቤቶች እና የጤና ተቋማት ከአገልግሎት ውጭ ናቸው መባሉን ሰምተናል፡፡




ያሬድ እንዳሻው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page