top of page

ነሐሴ 10፣2016 - በኢትዮጵያ ህገ መንግስት ላይ እስከ መገንጠል የሚለው አንቀጽ 39 እንዲሻሻል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አጀንዳ አድርጎ ለምክክር ኮሚሽን አቀረበው

  • Aug 16, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ህገ መንግስት ላይ እስከ መገንጠል የሚለው አንቀጽ 39 እንዲሻሻል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አጀንዳ አድርጎ ለምክክር ኮሚሽን አቀረበው፡፡


ክልሉ ሐምሌ 23 ቀን ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ አድርጎ ካቀረባቸው ጉዳዮች መካከል ውስጥ በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 39 የራስን እድል በራሱ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል የሚለው በሚደረገው ሀገራዊ ምክክር አንዲሻሻል ጠይቋል፡፡


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ልማት ማህበራት ህብረት ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ፋንታሁን መለሰ ህገ-መንግስቱ በሙሉ ሳይሆን አንቀጽ 39 ጨምሮ ሁሉን የማያስማሙ አንቀጾች እንዲሻሻሉ አጀንዳ አርገን ለኮሚሽኑ አቅርበናል ብለውናል፡፡


የሰንደቅ ዓላማ ጉዳይ እና የክልል አደረጃጀቶችን በተመለከተ ክልሉ ካቀረባቸው አጀንዳዎች መካከል ናቸው ተብሏል፡፡


አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያለቸው የህብረተሰብ ከፍሎች በፖለቲካው ላይ ውክልና እንዲኖራቸው እና የፖለቲካ አመራሮች በስልጣን ላይ የሚኖራቸው ቆይታ ገደብ እንዲኖረው የሚያደርግ ሥርዓት መዘርጋትም እንዱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አጀንዳ ነው ተብሏል፡፡


አንዱን የሚያጎላ ሌላውን የሚያሳንስ ሌላውን ዝቅ አድርጎ አንዱን ከፍ የሚደርጉ ትርክቶች እና ታሪኮቸም በምክክሩ እንዲታዩ አጀንዳ አድርገን ጠይቀናል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ልማት ማህበራ ህብረት ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ፋንታሁን መለሰ ንግረውና፡፡


ባንዲራ ህገ-መንግስት፣ የክልል አደረጃጀት እና መሰል አጀንደዎች ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተጨማሪ አዲስ አበባም አጀንዳዎቼ ናቸው ማለቱን መዘገባቸው ይታወሳል፡፡





ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page