top of page

ነሀሴ 27 2017 - በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተሰማርተው ሶፍትዌሮችን እያበለፀጉ ለተቋማት የሚያቀርቡ ድርጅቶች እየበረከቱ ነው

  • sheger1021fm
  • Sep 2
  • 1 min read

በቴክኖሎጂው ዘርፍ ተሰማርተው ሶፍትዌሮችን እያበለፀጉ ለተቋማት የሚያቀርቡ ድርጅቶች እየበረከቱ ነው፡፡


የድርጅቶቹ በዘርፉ መሰማራት የቴክኖሎጂው ዘርፍ ያለበትን እጥረት ያቃልላል ተብሏል፡፡


ወደእዚህ ዘርፍ እየመጡ ካሉ ተቋማት መካከል እንደሆነ የሚናገረው የአሜሪካ ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ሶፍትዌሮችን እያበለፀገ ለባንኮች፣ ለአቪየሽን ዘርፍ ድርጅቶች እንዲሁም ለሌላውም እያቀረበ ይገኛል።

ree

በሃገሪቱ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ክፍተት አለ ብለን ስለምናምን አሜሪካ ከሚገኘው ማሃሪሽ ኢንተርናሽናል ዩንቨርሲቲ ጋር በመተባበር የቴክኖሎጂ የትምህርት ዓይነቶች ላይ ትኩረት አድርገን እያስተማርን ነው ብለውናል።


በዚህም ከትምህርቱ ጎን ለጎን በሚይዟቸው ፕሮጀክቶች ለመንግስት ተቋማት፣ ለባንኮችና በአቬሽኑ ዘርፍ ላሉ ድርጅቶች ሶፍትዌሮችን እንደሚያበለፅጉና ተማሪዎቻውም ከተመረቁ በኋላ ወደዚህ ስራ እንደሚቀላቀሉ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አጥናፉ አስረድተዋል።


ከዚህም በተጨማሪ ኮሌጁ የኦላይን ትምህርቶችን የሚያስተምርበት STA አካዳሚ የተሰኘ ሶፍትዌር እንዳለው የሚናገሩት ፕሬዝዳንቱ ይህም እስካሁን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች የኦላይን ስልጠና ወስደው ሰርተፊኬት ያገኙበት መሆኑንም ጠቁመዋል።


የወቅቱ የትምህርት ዘርፍ ትልቁ ችግር ጥራት ነው፤ ኮሌጁ ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ ማስቻል ነው ያሉት ፕሬዝዳቱን በዚህ መንገድ አገኘነው ያሉትን ውጤትም ነግረውናል፡፡


ከ7 ዓመት በፊት ስራው ሲጀመር ዓላማችን አሜሪካ የሚገኘውን ማሃሪሽ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲን ኢትዮጵያ ውስጥ መክፈት ነበር ያሉት ዶ/ር አጥናፉ በራሱ ስም እዚህ ዩኒቨርሲቲ መክፈት ስለማይቻልና በአሜሪካ ያለውን የትምህርት ጥራት እዚህ ማምጣት ስለምንፈልግ ስሙን ተውሰን አሜሪካ ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ብለነዋል ሲሉም አስረድተዋል።


ኮሌጁ በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን፣ በሊደር ሺፕና በፕሮጀክት ማኔጅመንት በቅድመ ምረቃና ድህረ ምረቃ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 350 ተማሪዎች ባሳለፍነው ቅዳሜ አስመርቋል።


ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page