top of page

ነሀሴ 20 2017 - ''አፍሪካ ውስጥ ያለው የትምህርት ምዘና ሥርዓት ወጥ ለማድረግ የሚያስችል ማዕቀፍ እየተዘጋጀ ነው'' የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

  • Aug 26, 2025
  • 1 min read

አፍሪካ ውስጥ ያለው የትምህርት ምዘና ሥርዓት ወጥ ከተደረገ ሰዎች ወደ የትኛውም የአህጉሪቱ ክፍል ሄደው የጀመሩትን ትምህርት እንዲቀጥሉ ይረዳል ሲል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተናገረ፡፡


የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዳለው አሁን ባለው የምዘና ሥርዓት አንድ ተማሪ ከኢትዮጵያ ወጥቶ በሌሎች የአፍሪካ ሀገር ትምህርቱን ካቆመበት ለመቀጠል ይቸገራል፡፡


የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ(ዶ/ር) አፍሪካ ውስጥ ያለው የትምህርት ምዘና ሥርዓት ወጥ ለማድረግ የሚያስችል ማዕቀፍ እየተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡


ይህ ማዕቀፍ ለመተግበር እንዲቻል እየተደረገ ባለው የአፍሪካ የትምህርት ምዘና ጉባኤ ምክክር ይደረግበታል ያሉ ሲሆን ተሳታፊ ሀገራትም በአፍሪካ ህብረት በኩል ሀገራቸው ውስጥ እንዲተገበር ለማድረግ ቃል የሚገቡበት ነው ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ጨምሮ በሌሎች የአለም ሀገራት በምዘና ሥርዓት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮች የፈተና ስርቆት፣ ምዘናዎች ደረጃቸውን ጠብቀው አለመዘጋጀት እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው ይላሉ ዶክተር እሸቱ፡፡


የትምህርት ምዘና የሚደረገው አንድ ተማሪ ምን ያህል አውቋል? የሚለውን ለመገንዘብና ተማሪው ያለበት ክፍተቶችን እንዲገነዘብ ለማድረግ ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ጨምሮ በሌሎች ሀገራት ያለው ግንዛቤ ግን ምዘና ሲባል የመውደቅና የማለፍ ብቻ ተደርጎ ይታያል ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለው 41ኛው የአፍሪካ የትምህርት ምዘና ጉባኤ እስከ አርብ ድረስ የሚቀጥል ሲሆን 30 የአፍሪካ ሀገራት በጉባኤው እየተሳተፉ ነው፡፡


በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page