top of page

ነሀሴ 15 2017 - የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መጪው ምርጫ በወቅቱ እንዲካሄድ የሚያስችል ውይይት ጀምሪያለሁ አለ።

  • sheger1021fm
  • Aug 21
  • 1 min read

ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያሳትፍ የምርጫ ፍኖተ ካርታ እየተዘጋጀ እንደሚገኝም የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሠለሞን አየለ ተናግረዋል።


60 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በጋራ የያዘው ምክር ቤቱ እንደ ሀገር ያለውን የሠላም ሁኔታ መገምገሙንም ጠቅሷል።


ሁሉም ሃይሎች ለሠላም ቅድሚያ ሰጥተው እንዲሰሩ ከመግባባት ላይ መደረሱን አቶ ሠለሞን ጨምረው ነግረውናል።


በ2018 ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ በጀት ከማፀደቅ አንስቶ በተለያዩ ከተሞች የምርጫ ጣቢያ ልየታዎች እያደረግሁ ነው ማለቱ ይታወሳል።


የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page