top of page

ነሀሴ 1፣2016 - ገዳ ባንክ ከሳንቲም ፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽን አ.ማ ጋር በመሆን የፈጣን ምላሽ ኮድ(ኪው አር ኮድ) የተሰኘውን አገልግሎት ጀምሬአለሁ አለ፡፡

ገዳ ባንክ ከሳንቲም ፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽን አ.ማ ጋር በመሆን የፈጣን ምላሽ ኮድ(ኪው አር ኮድ) የተሰኘውን አገልግሎት ጀምሬአለሁ አለ፡፡


ከገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ ዲጂታል እና የዘመናዊ ግብይት ተጠቃሚ የሆነ ማህበረሰብን ለማብዛት እንዲሁም የክፍያ ሥርዓትን ለማዘመን ያግዛል የተባለለት የፈጣን ምላሽ ኮድ ወይም ኪው አር ኮድ የተሰኘው የክፍያ ሥርዓት ወደ አገልግሎት መግባቱን ባንኩ እወቁልኝ ብሏል፡፡

ወደ ስራ የገባው ይሄው የክፍያ ሥርዓት ለሆቴሎች፣ ለካፌዎች፣ ለሱቆች እና ለሌሎች የቢዝነስ ተቋማት የሚያገለግል መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው ከሱ በተጨማሪም በኦንላይን ለሚሰሩ ነጋዴዎችም ሆነ ተጠቃሚዎችም የሚያገለግል ነው ይላሉ፡፡


በገዳ ባንክ እና በሳንቲም ፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽን አ.ማ ይፋ የሆነው የፈጣን ምላሽ ኮድ ወይንም ኪው አር ኮድ አገልግሎት ነጋዴው እና ባንኩን የሚያግዝ ነው ተብሎለታል፡፡


በተጠናቀቀው በጀት አመት ባንኩ ጠቅላላ ሀብቴ ወደ 5.3 ቢሊየን ብር አድጓል ያለ ሲሆን ከደንበኞቼ የሰበሰብኩት ገንዘብ ደግሞ ከ4 ቢሊየን ብር በላይ ነው ብሏል፡፡


ገዳ ባንክ ወደ ስራ ከገባ 18 ወራት ተቆጥረዋል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page