top of page

ነሀሴ 1፣2016 - በዋግህምራ ዞን በዘንድሮ የክረምት ወቅት ዝናብ ቢያገኝም በአንዳንድ አካባቢዎች ከፍተኛ ዝናብ በማጋጠሙ ለእንስሳት ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል

  • Aug 7, 2024
  • 1 min read

ባለፉት ሶስት ዓመታት ዝናብ ጠብ ባለማለቱ እና በድርቅ ሲፈተን የቆየው የዋግህምራ ዞን በዘንድሮ የክረምት ወቅት ዝናብ ቢያገኝም በአንዳንድ የዞኑ አካባቢዎች ከፍተኛ ዝናብ በማጋጠሙ ምክንያት ለእንስሳት ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡


የነዋሪዎች ቤትም በላያቸው ላይ መፍረሱን ሰምተናል፡፡


በዞኑ በአንዳንድ ወረዳዎች ከፍተኛ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ ጎርፍ እንደተከሰተ የተነገረ ሲሆን በዚህም 80 የሚሆኑ እንሰሳት በጎርፍ መወሰዳቸውን ሸገር ሰምቷል፡፡


ከዚህ በተጨማሪም በርከት ያለ ሄክታር ላይ የበቀሉ #ሰብሎች ላይ ጉዳት ማድረሱን የተናገሩት የዞኑ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ምህረት መላኩ ይህ ደግሞ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ዞንኑ ያሰጋዋል ብለዋል፡፡


ቀደም ሲል ክረምቶችን ሲቋቋሙ የቆዩ ተራሮች እና የነበሩ ተፋሰሶች ዞኑ አጋጥሞት በቆየው #የሰላም _እጦት ድርቅ እና ሌላ ሌላውም ችግር አሁን ላይ ከፍተኛ ዝናብን የመቋቋም አቅም አሳጥቶታል ብለዋል ሃላፊው፡፡


ላለፉት ሶስት አመታት ዝናብ ጠብ ያላለበት የዋግህምራ ዞን በረሀብ በተለያዩ ወረርሽኞች እና በሰላም እጦት ሲፈተን መቆየቱ ይታወቃል፡፡


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page