ባለፉት ሶስት ዓመታት ዝናብ ጠብ ባለማለቱ እና በድርቅ ሲፈተን የቆየው የዋግህምራ ዞን በዘንድሮ የክረምት ወቅት ዝናብ ቢያገኝም በአንዳንድ የዞኑ አካባቢዎች ከፍተኛ ዝናብ በማጋጠሙ ምክንያት ለእንስሳት ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡
የነዋሪዎች ቤትም በላያቸው ላይ መፍረሱን ሰምተናል፡፡
በዞኑ በአንዳንድ ወረዳዎች ከፍተኛ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ ጎርፍ እንደተከሰተ የተነገረ ሲሆን በዚህም 80 የሚሆኑ እንሰሳት በጎርፍ መወሰዳቸውን ሸገር ሰምቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በርከት ያለ ሄክታር ላይ የበቀሉ #ሰብሎች ላይ ጉዳት ማድረሱን የተናገሩት የዞኑ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ምህረት መላኩ ይህ ደግሞ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ዞንኑ ያሰጋዋል ብለዋል፡፡
ቀደም ሲል ክረምቶችን ሲቋቋሙ የቆዩ ተራሮች እና የነበሩ ተፋሰሶች ዞኑ አጋጥሞት በቆየው #የሰላም _እጦት ድርቅ እና ሌላ ሌላውም ችግር አሁን ላይ ከፍተኛ ዝናብን የመቋቋም አቅም አሳጥቶታል ብለዋል ሃላፊው፡፡
ላለፉት ሶስት አመታት ዝናብ ጠብ ያላለበት የዋግህምራ ዞን በረሀብ በተለያዩ ወረርሽኞች እና በሰላም እጦት ሲፈተን መቆየቱ ይታወቃል፡፡
Comments