top of page

ቻይና የኢትዮጵያ ቡና 3ኛዋ ትልቅ ገዥ ሆነች።

  • Jun 18
  • 1 min read

ሰኔ 11/2018


ቻይና የኢትዮጵያ ቡና 3ኛዋ ትልቅ ገዥ ሆነች።


2ኛው የጋራ የቡና ኤግዚቢሽንም ሊካሄድ ነው መሆኑን የቡናና ሻይ ባለስልጣን ተናግሯል።


የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች ‹ጁጆ ሎጂስቲክስ› ከተባለው የቻይና ኩባንያ ተወካዮች ጋር በዋና መስሪያ ቤታቸው ተቀብለው ውይይት አድርገዋል።


በውይይቱም የሁለቱ ሀገራት የቡና ንግድ ትስስር እያሳየ የመጣው ከፍተኛ ዕድገትና ቀጣይ የትብብር ዕድሎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።



የቻይናው ኩባንያ ተወካዮች ባሳለፍነው ዓመት የመጀመሪያው የኢትዮ-ቻይና የቡና ኤግዚቢሽን በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን አስታውሰዋል።


በወቅቱ የኢትዮጵያ ባህላዊ የቡና አፈላል ሥነ-ሥርዓት ቀርቦ ምርቱን የማስተዋወቅ ትልቅ ሥራ መሠራቱን የጠቀሱት ተወካዮቹ፣ በዕለቱም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር ) ተገኝተው እንደነበር ጠቅሰዋል።


2ኛው የኢትዮ-ቻይና የቡና ኤግዚቢሽን በመጪው መስከረም 15 ቀን እንደሚካሄድ ተነግሯል።


በመጀመሪያው ዝግጅት ላይ የኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ ተዋናዮች ተሳትፎ አነስተኛ እንደነበር አንስተዋል።



በመሆኑም በዘንድሮው ሁለተኛ ዙር ዝግጅት ላይ የሀገሪቱ የቡና ላኪዎች፣ አምራቾችና መላው የቡናው ማኅበረሰብ በስፋትና በበቂ ሁኔታ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።


የቡናና ሻይ አመራሮች በበኩላቸው ቻይና ለኢትዮጵያ ቡና ለሰጠችው ከፍተኛ ቦታና ለምታደርገው የማስተዋወቅ ሥራ አድንቀዋል።


በሁለተኛው ኤግዚቢሽን ላይ ባለስልጣኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግና የሀገር ውስጥ የቡና ተዋናዮች በስፋት እንዲሳተፉ የበኩሉን የቅስቀሳ ሚና እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።


ባለፈው ዓመት የኢትዮጵያን ቡና በመግዛት 7ኛ ደረጃ ላይ የነበረችው ቻይና፣ ዘንድሮ 3ኛ ደረጃ ላይ መገኘቷ ተጠቅሷል።


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page