top of page

ታህሳስ 9፣2017 - ''ከምክክሩ በኋላ በኦሮሚያ ለብዙ ምስቅልቅል ምክንያት የሆነው ግጭት ይቆማል የሚል ተስፋ አለን'' የምክክር ተሳታፊዎች

  • sheger1021fm
  • Dec 18, 2024
  • 1 min read

ከሀገራዊ ምክክሩ በኋላ በኦሮሚያ ክልል ለብዙ ምስቅልቅል ምክንያት የሆነው ግጭት ይቆማል የሚል ተስፋ አለን ሲሉ የምክክር ተሳታፊዎች ተናገሩ።


ተሳታፊዎቹ ይህን የተናገሩት ዛሬ በአዳማ ከተማ ሦስተኛ ቀኑን በያዘው የምክክር ምዕራፍ ላይ ነው።


በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የምክክር መድረክ ተሳታፊዎችን ከምክክሩ ምን እንደሚጠብቁ ጠይቀናቸዋል።


ተሳታፊዎቹ ‘’ከምክክሩ ቡኋላ በክልሉ የቀጠለው ግጭት መፍትሔ ያገኛል ብለን እንጠብቃለን’’ ብለዋል።


ትምህርት እንዲቋረጥ፣ የጤና ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ ሰዎች ከቦታ ቦታ እንዳይቀሳቀሱ እንቅፋት የሆነው በክክሉ ያለው ግጭት ከምክክሩ ብኋላ መፍትሔ ያገኛሉ ብለን እንጠብቃለን ብለውናል።

ምክክሩ ውጤታማ እንዲሆንም ከምክክር ሂደቱ እራሳቸውን ያገለሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት እንዲካተቱ ማድረግ ከሀገራዊ ምክክር ኮምሽን ይጠበቃል ብለዋል።


ሀገራዊ ምክክር ኮምሽን በበኩሉ በተደጋጋሚ ሁሉም አካላት በምክክሩ እንዲሳተፉ ተደጋጋሚ ጥሪዎችን እያደረኩ ነው ሲል መናገሩ ይታወሳል።


በአዳማ ከተማ ገልማ አባገዳ ውስጥ እየተካሄደ ባለው የምክክር ምዕራፍ ላይ ከ356 ወረዳዎች የተወከሉ ከ7,000 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተካፈሉ ይገኛሉ።


ያሬድ እንዳሻው



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page