top of page
  • sheger1021fm

ታህሳስ 8፣ 2015- የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የአርብቶ አደሩና አርሶ አደሩን ስራ ለመደገፍ እስካሁን ከ9.7 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ አድርጌያለው አለ


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የአርብቶ አደሩና አርሶ አደሩን ስራ ለመደገፍ እስካሁን ከ9.7 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ አድርጌያለው አለ።


ይንን ያህል ገንዘብ በማቅረብም በኢትዮዽያ ቀዳሚው ባንክ ሆኛለው ብሏል።


ባንኩ ከዓመታዊ ጉባኤው አስቀድሞ የሚያደርገውን የኅብረት ሥራ ማህበራት ቀንን በአዳማ አክብሯል።


የኅብረት ሥራ ማህበራት ቀኑ ለ4ኛ ጊዜ መከበሩን ከአቶ ደረጄ ወዳጆ የማህበራትና ደንበኞች ግንኙነት ዳይሬክተር ሠምተናል።


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ከ56 በመቶ በላይ የባንኩ ድርሻ በአርብቶና አርሶ አደሮች መያዙንና ባለቤቶቹም እነሱ መሆናቸው ተናግሯል።


በዝግጅቱ ላይ ሲነገር እንደሰማነው ባንኩ 9.7 ቢሊዮን ብር ለአርሶና አርብቶ አደሩ ስራ መደገፊያ ፋይናንስ በማድረግ በኢትዮዽያ ቀዳሚ ባንክ ሆኗል ተብሏል።


ገንዘቡ በግብርና ሜካናይዜሽን፣ በእህል፣ በቡና ምርት፣ በከብት እርባታ እና ማድለብ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለተሰማሩ ማህበራት፣ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች መቅረቡን ከአቶ ደረጄ ሰምተናል።


አርሶና አርብቶ አደሮች በማህበርና በዩኒየን ስር በመሆን ትልቁን የባንኩን ድርሻ እንደያዙ ተሠምቷል።


ባንኩ አንድ በመቶ ዓመታዊ ትርፉን የኅብረት ሥራ እና አርሶ አደሮችን ለማሰልጠን እንደሚያውልም ተነግሯል።


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በ2021/22 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የኅብረት ሥራ ማህበራት የተለያየ እውቅና እና ሽልማትን ተሰጥቷል።


ቴዎድሮስ ወርቁ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page