top of page
  • sheger1021fm

ታህሳስ 8፣ 2015- አገር አቀፍ የወጣቶች ምክር ቤት ለማቋቋም በተዘጋጀ የመነሻ ሰነድ ላይ በአዳማ ውይይት እየተካሄደ ነው


አገር አቀፍ የወጣቶች ምክር ቤት ለማቋቋም በተዘጋጀ የመነሻ ሰነድ ላይ በአዳማ ውይይት እየተካሄደ ነው።


የሚቋቋመው ምክር ቤት የወጣቶች ድምፅ በመሆን ለአባላቱ መብትና ጥቅም ይሰራል ተብሏል።


መንግስትን የማማከርና የመሞገት ሚና እንደሚኖረውም በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የወጣቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሙና አህመድ ተናግረዋል።


አገር አቀፍ የወጣቶች ምክር ቤት የማቋቋሙ አስፈላጊነት የታመነበት አሁን ባሉ የወጣት አደረጃጀቶች ላይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዳሠሣ ጥናት ከተካሄደ በኋላ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቅሰዋል።


እንደ እሳቸው አባባል አሁን ያሉ አደረጃጀቶች ለወጣቶች ድምፅ መሆን ላይ ክፍተት ይታይባቸዋል።


የአካታችነት ችግር እንደሚስተዋልባቸውም ሚኒስትር ዴኤታዋ የዳሠሣ ጥናቱን መነሻ አድርገው ተናግረዋል።


የሚቋቋመው አገር አቀፍ የወጣቶች ምክር ቤት ከፌዴራል እስከ ክልል ድረስ ተመሳሳይ መዋቅር ይኖረዋል ተብሏል።


የሌሎች ሀገራትን ልምድ ከግምት በማስገባት የሚቋቋም ምክር ቤት እንደሚሆንም ሠምተናል።


የውይይቱ ተሳታፊዎች ምክር ቤቱን ለማቋቋም በተዘጋጀው የመነሻ ሰነድ ላይ ሃሳብ እየሰጡ እንደሚገኙ ባልደረባችን ንጋቱ ረጋሣ ከአዳማ የላከልን መረጃ ያመለክታል።


ንጋቱ ረጋሳ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page