top of page

ታህሳስ 7፣2017 - የአንካራው ስምምነት የተደረሰውም ሰባት ሰዓታት ከፈጀ ስብስብ በኋላ መሆኑን ኤርዶሃን ተናግረዋል

  • sheger1021fm
  • Dec 16, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያና ሶማሊያን ያስማሙት የቱርኩ ፕሬዘዳንት ራሲፕ ታይፕ ኤርዶሃን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው፡፡


ኤርዶሃን ከሁለት ሳምንታት በኋላ በሚብተው የፈረንጆቹ 2025 የመጀመሪያዎቹ ሁለት ወራት ኢትዮጵያን እና ሶማሊያን እንደሚጎበኙ መናገራቸውን የቱርኩ አናዶሉ ፅፏል፡፡


ፕሬዘዳንት ኤርዶሃን የኢትዮጵያውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድንና የሶማሊያው ፕሬዘዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድን አሸማግለው ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የሶማሊያን ሉአላዊነት ባከበረ መልኩ እንዲሆን በሁለቱ ሀገራት በመሪዎች ደረጃ ባለፈው ሳምንት ስምምነት ተደርጓል፡፡


የአንካራው ስምምነት የተደረሰውም ሰባት ሰዓታት ከፈጀ ስብስብ በኋላ መሆኑን ኤርዶሃን ተናግረዋል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page