ታህሳስ 7፣ 2015- በፈረንሳይ ሊዮን ከተማ አቅራቢያ በአንድ የመኖሪያ ሕንፃ ላይ የተቀሰቀሰ ቃጠሎ 10 ሰዎችን መግደሉ ተሰማ
- sheger1021fm
- Dec 16, 2022
- 1 min read

በፈረንሳይ ሊዮን ከተማ አቅራቢያ በአንድ የመኖሪያ ሕንፃ ላይ የተቀሰቀሰ ቃጠሎ 10 ሰዎችን መግደሉ ተሰማ፡፡
በቃጠሎ ሕይወታቸው ከተቀጠፈው መካከል አምስቱ ሕፃናት እንደሆኑ ፍራንስ 24 ፅፏል፡፡
አራት ሰዎች ደግሞ በቃጠሎው ከባድ ጉዳት እንዳጋጠማቸው ተሰምቷል፡፡
ለሕይወታቸውም ያሰጋቸዋል ተብሏል፡፡
ቃጠሎውን በ170 የአደጋ ተከላካዮች ጥረት ማጥፋት እንደተቻለ ታውቋል፡፡
የቃጠሎው ምርመራ እንደሚከናወን በዘገባው ተጠቅሷል፡፡
የኔነህ ከበደ
ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Comments