top of page
  • sheger1021fm

ታህሳስ 7፣ 2015- በመንግስት ግዥና ጨረታ የሚሳተፉ አቅራቢዎች በገቡት ውል መሠረት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት ሊኖር ይገባል ተባለ

Updated: Dec 17, 2022



በመንግስት ግዥና ጨረታ የሚሳተፉ አቅራቢዎች በገቡት ውል መሠረት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት ሊኖር ይገባል ተባለ።


ይህ የተባለው በመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን እንዲሁም በመንግስት ግዢ አገልግሎት አሰራር ዙሪያ በተካሄዱ የቁጥጥር ስራዎች የተለዩ ግኝቶችና የመፍትሔ ሃሳቦች ዙሪያ በአዳማ ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ ነው፡፡


በሁለቱ ተቋማት አሰራር ዙሪያ ቁጥጥሩን አካሂዶ ግኝቶችን እና ምክረ ሃሳቦችን ለሚመለከታቸው በመድረኩ ይፋ ያደረገው የህዘብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ነው።


በመድረኩ ላይ ሲነገር እንደሠማነው በመንግስት ግዥና ጨረታ የሚሳተፉ አቅራቢዎች በገቡት ውል መሠረት ግዴታቸውን መወጣት ላይ ችግሮች አሉ።


የሚፈለገውን ዕቃ በወቅቱ ያለማቅረብ እና ጥራታቸው የተጓደሉ ምርቶችን ማስረከብ ከችግሮቹ መካከል እንደሆኑ ተነግሯል።


አቅም የሌላቸው አቅራቢዎች በመንግስት ግዢና ጨረታ እንዲሳተፉ የማድረግም ችግር እንዲሁ ተጠቅሷል።


ባሉት ቀነ ገደብ ዕቃዎችን የማያስረክቡ እንዱሉም ተነግሯል።

በወቅቱ በሚያስረክቡት ላይ በውሉ መሠረት እርምጃ ያለ መውሰድ ይታያልም ነዉ የተባለው።


አቅራቢዎችን ለመቆጣጠር ጠንካራ ስርዓት ሊዘረጋ እንደሚገባ የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በምክረ ሃሳቡ ጠቅሷል።


ንጋቱ ረጋሳ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page