top of page

ታህሳስ 6፣ 2015- በኢትዮጵያ 68 በመቶ የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች እና 51 በመቶ የሶስተኛ ክፍል ተማሪዎች ማንበብ እንደማይችሉ ጥናት አሳየ

  • Dec 15, 2022
  • 1 min read

በኢትዮጵያ 68 በመቶ የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች እና 51 በመቶ የሶስተኛ ክፍል ተማሪዎች ማንበብ እንደማይችሉ ጥናት አሳየ።


ጥናቱ ያከናወነው ራይዝ ኢትዮጵያ በአለም ባንክ የሚደገፍ እና አለምአቀፍ የምርምር ፕሮግራም ሲሆን በትምህርት ጥራት ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የተቋቋመ ድርጅት መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተናግሯል።


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ እና የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲቱት በጋራ በመሆን ጥትት እና ምርምሩን የሚያካሄዱ ተቋሟት ናቸው ተብሏል።


በዛሬው እለት የጥናት ውጤቱ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አዘጋጅነት በሂልተን ሆቴል ቀርቧል።


በኢትዬጲያ በተለያዩ የአንደኛ ደረጃ 168 ትምህርትቤቶች በሚገኙ በ 9,000 ተማሪዎች በተጠናዉ ጥናት መሰረት 2ኛ ክፍል ተማሪዎች 68% እና 3ኛ ክፍል ተማሪዎች 51% ያህሉ ማንበብና መጻፍ እንደማይችሉ ጥናቱ አሳይቷል።


የተማሪዎችን የትምህርት ዉጤት ለማሻሻል የትምህርት ስርአቱ የተናበበ እና የተቀናጀ ትግበራ አስፈላጊ እንደሆነ በጥናቱ ላይ ተጠቅሷል ተብሏል።


ንጋቱ ሙሉ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 
 
 

Recent Posts

See All
የሐምሌ 15 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሞሪታንያ በሞሪታንያ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ በደረሰ የባህር አደጋ 144 ጥገኝነት ፈላጊዎቹ ሳይሞቱ አልቀረም ተባለ፡፡ የአደጋው ሟቾች መነሻዋን ከጋምቢያ በማድረግ ወደ ስፔን በማምራት ላይ በነበረች ጀልባ የተሳፈሩ ጥገኝነት ፈላጊዎች እንደሆኑ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በጀልባዋ ተሳፍረው የነበሩት በሙሉ ከተለያዩ የአፍ

 
 
 
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡

ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page