top of page

ታህሳስ 6፣ 2015- በቻድ በረሃ ውስጥ የ27 ስደተኞች አፅም ተገኘ


በቻድ በረሃ ውስጥ የ27 ስደተኞች አፅም ተገኘ፡፡


የስደተኞቹ አፅም የተገኘው በአንድ ፒክ አፕ መኪና ላይ እንደሆነ አለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ባለስልጣናት መናገራቸውን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


አፅማቸው የተገኘው ስደኞች የሞቱት ከዓመት ከ5 ወራት በፊት በጉዞ ላይ በነበሩበት ወቅት እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡


ይጓዙባት የነበረች ፒክ አፕ መኪና መበላሸቷ በረሃ ላይ እንዳስቀራቸው ተገምቷል፡፡


በዚህ በረሃማ ስፍራ ረሃብ እና የውሃ ጥም ለሕልፈታቸው ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ ተጠርጥሯል፡፡


IOM በነዚህ ስደተኞች መጥፎ ዕጣ ፈንታ በእጅጉ አዝኛለሁ ማለቱ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page