top of page

ታህሳስ 5፣2017 - ’ክፍለ ከተማው ምትክ ቦታ ሳይሰጣችሁ እንዳትወጡ ቢለንም ወረዳው በተኛንበት መጥቶ ቤታችን አፈረሰብን’’

  • sheger1021fm
  • Dec 14, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ተክለሃይማኖት አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ‘’አካባቢው ለልማት እንደሚፈለግ ተነግሮን፣ ምትክ ቤት እንዲሰጠን ተስማምተን፣ እየጠበቅን እያለን ዛሬ ማለዳ ቤታችንን መፍረስ ጀምሯል’’ አሉ፡፡


‘’ክፍለ ከተማው ምትክ ቦታ ሳይሰጣችሁ እንዳትወጡ ቢለንም ወረዳው በተኛንበት መጥቶ ቤታችን አፈረሰብን’’ ሲሉ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የተክለሓይማኖት አካባቢ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ነገረውናል፡፡


ነዋሪዎቹ ቦታው ለልማት እንደሚፈለግ ተነግሮን እኛም ተስማምተን፣ ምትክ ቦታ በመጠበቅ ላይ እያለን ወረዳው ዛሬ ማለዳ ቤታችንን በድንገት አፈረሰብን ሲሉ ቅሬታቸውን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አቅርበዋል፡፡


ክፍለ ከተማው ‘’አዎ ምትክ ቤት ሳይሰጣቸው ቤታቸው እንደማይፈርስ ቃል ገብቻለሁ፣ ቤቶቹ እየፈረሱ ስለመሆኑም የማውቀው ነገር የለም’’ ብሏል፡፡


ወረዳው በበኩሉ ‘’ለነዋሪዎቹ ምት ቦታ እንደተሰጣቸው እና እንዳፈርስ ከክፍለ ከተማው ትዕዛዝ ስለሰጠኝ ነው ያፈረስኩት ብሏል፡፡


ምትክ ቤት መሰጠቱን ማረጋገጥ የኔ ሃላፊነት አይደለም ሲልም፡፡


አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በበኩሉ ቤቶቹ እንዲርሱ እንዳላዘዘና ስለመፍረሳቸውም መረጃው እንደሌለው ተናግሯል፡፡





ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page