top of page

ታህሳስ 4፣ 2015- የኩዌት ፓርላማ የተጭበረበረ የግብፅ ዩኒቨርስቲዎች ዲግሪዎችን የያዙ ከ140 በላይ ሰዎች ላይ ደረስኩባቸው አለ

  • sheger1021fm
  • Dec 13, 2022
  • 1 min read

የኩዌት ፓርላማ የተጭበረበረ የግብፅ ዩኒቨርስቲዎች ዲግሪዎችን የያዙ ከ140 በላይ ሰዎች ላይ ደረስኩባቸው አለ፡፡


የፓርላማው የትምህርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩን እያጣራው መሆኑን ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡


የዚህ ሐሰተኛ ዲግሪ አሰራጮች እነማን እንደሆኑ ክትትሉን አበርትቶታል ተብሏል፡፡


በዚሁ ጉዳይ መነሻ ነዋሪነቱ በኩዌት የሆነ ግብፃዊ ተይዞ መታሰሩ ታውቋል፡፡

የግለሰቡ መያዝ የዚህን የወንጀል መረብ ጥልፍልፎች ለመፍታት ፍንጭ እንደሚሰጥ ታምኖበታል ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page