top of page

ታህሳስ 4፣ 2015- በናይጀሪያ ኢሞ ግዛት በምርጫ ፅህፈት ቤት ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ ታጣቂዎች ሶስቱ በፖሊስ መገደላቸው ተሰማ፡፡

ታህሳስ 4፣ 2015


በናይጀሪያ ኢሞ ግዛት በምርጫ ፅህፈት ቤት ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ ታጣቂዎች ሶስቱ በፖሊስ መገደላቸው ተሰማ፡፡


በፖሊስ የአፀፋ ተኩስ ከተገደሉት ሌላ ሁለቱ በስፍራው እንደተያዙ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


በታጣቂዎቹ ጥቃት የግዛታዊ የምርጫ ፅህፈት ቤቱ ሕንፃ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል፡፡


በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ላይ ስለደረሰው ጉዳት የተጠቀሰ ነገር የለም፡፡


በኢሞ ግዛት በምርጫ ፅህፈት ቤቶች ላይ ጥቃት ሲሰነዘርባቸው በ2 ሳምንታት ጊዜ ይሄ 3ኛው ነው ተብሏል፡፡


ናይጀሪያ በመጪው የካቲት ወር ፕሬዝዳንታዊ፣ የግዛት እና የፓርላማ ምርጫ ለማካሄድ እየተዘጋጀች ነው፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page