top of page

ታህሳስ 3፣ 2015- በጣሊያን ሮም በአንድ ካፌ ውስጥ በተከፈተ ተኩስ ሶስት ሴቶች መገደላቸው ተሰማ

Updated: Dec 13, 2022


ታህሳስ 3፣ 2015


በጣሊያን ሮም በአንድ ካፌ ውስጥ በተከፈተ ተኩስ ሶስት ሴቶች መገደላቸው ተሰማ፡፡


የተገደሉት ሴቶች በመኖሪያ አካባቢ ምክክር ላይ ነበሩ ተብሏል፡፡


የነዋሪዎች ኮሚቴዎች ወኪሎች እንደነበሩ TBP በድረ ገፁ ፅፏል፡፡


በጥቃቱ ከተገደሉት ሌላ 4 ሰዎች ደግሞ አካላዊ ጉዳት ገጥሟቸዋል ተብሏል፡፡


የ57 አመቱ ጥቃት አድራሽ ከመኖሪያ አካባቢ ማህበር የቦርድ አባሎች ጋር ተወዛጋቢ ነበር መባሉ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ግለሰቡ ጥቃቱን ከፈፀመ በኋላ በፖሊስ ተይዞ መታሰሩ ታውቋል፡፡ በጥቃቱ ከተገደሉት መካከል አንደኛዋ የጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ጓደኛ ነበረች ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page