ታህሳስ 25፣2016 - እየተገነባ ያለው የፎረንሲክ ምርመራ ማዕከል በቅርቡ ወደ ስራ ይገባል ተባለ፡፡
- sheger1021fm
- Jan 4, 2024
- 1 min read
እየተገነባ ያለው የፎረንሲክ ምርመራ ማዕከል በቅርቡ ወደ ስራ ይገባል ተባለ፡፡
የፖሊስን ስነ ምግባር የሚሸረሽሩ ስራዎች ለማስተካከል እየተሰራ ነው ተባለ፡፡
ይህ የተባለው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 99 ኢንስፔክተሮችን በዋና ኢስፔክተርነት ባስመቀረበት ወቅት ነው፡፡
የተመረቁት ዋና ኢንስፔክተሮች በዘመናዊ መንገድ ወንጀል ምርመራ እና ሌሎች የተለያዩ ስልጠናዎች ወስደዋል ተብሏል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል እንዳሉት ኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፖሊስ ኢንስቲትዩት እየገነባች ነው።
ይህም ለሀገሪቱ ፖሊስ እድገት ትልቅ በር ይከፍታል ብለዋል፡፡
ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ የፌደራል ፖሊስ ወንጀልን ለመከላከል የሚረዳ መተግበሪያ እያለማ ነው ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡ በቀላሉ በመተግበሪያ ከተቋሙ ጋር በመገናኘት ወንጀልን መከላከል ይችላል ብለዋል፡፡

ባለፉት ዓመታት የፖሊስ ስነ ምግባር የሚሸረሽር ስራዎች ተሰርተዋል የተባለ ሲሆን አሁን ላይ ፌደራል ፖሊስ ይህንን ለማስተካከል እየሰራ ነው ተብሏል።
የፌደራል ፖሊስ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን የሀገሪቱን ሰላም ለማስጠበቅ እየሰራ ነው መባሉንም ሰምተናል።

የመጀመሪያው የፖሊስ አዛዥ የብርጋዴር ጀነራል ፅጌ ዲቦ ሀውልትም በዚሁ ወቅት ተመርቋል፡፡
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Comentarios