ኢትዮጵያ ሰላሟን ፍለጋ የሰላም ሚኒስቴርን እስከማቋቋም ተጉዛለች፡፡
ግን ዛሬም ሰላም ብርቅ የሆነባቸው አካባቢዎች በርካታ ናቸው፡፡
#ሰላም ግን እንዴት ይመጣል?
ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት የግጭት አዙሪት እንድትወጣ ምን ቢደረግ ይሻላል?
ሰላም በሀገሪቱ እንዲሰፍን ያግዛሉ ተብለው የተቋቋሙ መስሪያ ቤቶች እርስ በእርሳቸው ተመጋጋቢ ሆነው ሰላምን ለማስፈን እየሰሩ ነው ወይ?
እነዚህ የተነሱ እና ሌሎች ጥያቄዎችን ለመመለስ የሰላም ፍኖተ ካርታ ሳያስፈልግ አይቀርም ያሉን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና የአለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ ዮናስ አሽኔ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
መምህሩ አሁን ላይ በተቋማት ደረጃ ያለው የሰላም ግንባታው የተበታተነ ይመስላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
コメント