top of page

ታህሳስ 23፣2017 - ‘’75 በመቶው የተቋሙ ደንበኛ የ1፣ የ3 እና የ5 ብር ፓኬጅ የሚሞላ ነው’’ ኢትዮ ቴሌኮም

  • sheger1021fm
  • Jan 1
  • 1 min read

ኢትዮ ቴሌኮም ተግባራዊ ያደረግሁት የታሪፍ ማሻሻያ 75 በመቶ ተጠቃሚዎችን የሚመለከት አይደለም አለ፡፡


ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ በፓርላማው ተገኝተው ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ ለቀረቡ ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ 75 በመቶው የተቋሙ ደንበኛ የ1፣ የ3 እና የ5 ብር ፓኬጅ የሚሞላ ነው ብለዋል፡፡


የተጠቀሱትን የገንዘብ መጠን የሚጠቀሙት ላይም ምንም ዓይነት የታሪፍ ጭማሪ አልተደረገም ብለዋል፡፡


ባለፉት 6 ዓመታት ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው በአነስተኛ ታሪፍ እንደነበር ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል፡፡


ይሁንና የማክሮ ኦኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ለብዙዎች የማስፋፊያ ስራዎችን የምንገዛቸውን አገልግሎቶች ግዥ የምንፈፅመው በዶላር በመሆኑ ታሪፍ ለማሻሻል ተገደናል ሲሉ አስረድተዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page