top of page

ታህሳስ 23፣2017 - ''በነበረው ግጭት 128 የጤና ተቋማት ሙሉ ብሙሉ እና በከፊል ወድመውብኛል'' የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል

በነበረው ግጭት ምክንያት 128 የጤና ተቋማት ሙሉ ብሙሉ እና በከፊል ወድመውብኛል ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተናገረ፡፡


በክልሉ አሁን ሰላም ስለሰፈነ የወደሙ የጤና ተቋማትን በማቋቋሙ እርዱኝ ብሏል፡፡


#መተለከል እና #ካማሺ ዞኖች ደግሞ በግጭቱ ይበልጥ የጤና ተቋማት የወደሙባቸው ናቸው ተብሏል፡፡


ይህንን የነገሩን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አለም ደበሎ ናቸው፡፡


የደረሰው ጉዳት ተጠንቶ ለፌዴራል መንግስት ሪፖርት ተድርጓልም ብለውናል ሀላፊው፡፡


ነገር ግን በጤና ተቋማቱ የደረሰው ውድመት በመንግስት አቅም ብቻ መልሶ ለመገንባት የሚከብድ እንደሆነ አንስተዋል፡፡

ስለሆነም የቻለ ሁሉ በ #ህክምና_መሳሪያም ሆነ በሌላው ቢረዳን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡


በተለይ ከሁለት ዓመት በፊት የማንገባባቸው ወረዳዎች ነበሩ ሲሉ ተናግረዋል አቶ አለም፡፡


አሁን ግን ባለሞያዎች እየተመደቡ የጤና አገልግሎት በተለያዩ ቦታዎች እንደተጀመሩ ጠቅሰዋል፡፡

ለጤና ተቋማቱ ውድመት ምክንያት የነበረው #የጸጥታ_ችግር ተፈትቶ አሁን ላይ ሰላም ወርዷል ብለዋል፡፡


የቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለዓመታት በዘለቀ ግጭት ውስጥ እንደነበረ ይታወሳል፡፡


በዚህም የጤና፣ የትምህርት አገልግሎትን ጨምሮ የበዙ ማህበራዊ መስተጓጉሎች አጋጥመው እንደቆዩ ተነግሮ ነበረ፡፡


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የክልሉ መንግስት ጫካ ከነበሩ ታጣቂዎች ጋር ስምምነት ፈጥሬ ሰላም ወርዷል ብሏል፡፡


ከታጣቂዎቹ መካከልም በካቢኔነት ጭምር ሾሜም አብረን እየሰራን ነው ማለቱ ይታወሳል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ማንያዘዋል ጌታሁን ያዘጋጀውን በፋሲካ ሙሉወርቅ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page