top of page

ታህሳስ 21፣2017 ''ካሉ አካል ጉዳተኛ ህፃናት ውስጥ ከ85 እስከ 90 በመቶ የሚሆኑት የትምህርት እድል እያገኙ አይደለም'' ኢሰመኮ

  • sheger1021fm
  • Dec 30, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ካሉ አካል ጉዳተኛ ህፃናት ውስጥ ከ85 እስከ 90 በመቶ የሚሆኑት የትምህርት እድል እያገኙ አይደለም ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡


ለአካል ጉዳተኞች የመማሪያ ቦታ፣ መምህር የለንም በሚል ትምህርት ቤቶች አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች አይቀበሉም ተብሏል፡፡


የኢሰመኮ የሴቶች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋሪያ ወላጆች አካል ጉዳተኛ ሕፃናትን ወደ ትምህርት ቤት ሊያስመዘግቡ ሲሄዱ የግልም ሆነ የመንግስት ትምህርት ቤቶች አንቀበልም ብለው እንደሚመልሷቸው በተለያዩ ጊዜያቶች ወላጆች አቤቱታቸው ለኮሚሽኑ እንደሚያቀርቡ ነግረውናል፡፡


ኮሚሽኑም በጉዳዩ ላይ ትምህርት ቤቶችን ሲጠይቅ የአቅም ችግር አለብን ይላሉ ያሉት ኮሚሽነር ርግበ በትምህርት ቤቶች በኩል የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ አይደለም፣ እንዲያርሙም እየጠየቅን ነው ብለዋል።


በቤተሰብ እና በራሳቸው ጥራት ተምረው ወደ ስራው አለም የተቀላቀሉ አካል ጉዳተኞች እንደማንኛውም ዜጋ ታክስ የሚከፍሉ ቢሆንም በአገልግሎት እኩል ተጠቃሚ አለመሆናቸውን ኮሚሽነር ርግበ ተናግረዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….



ፍቅሩ አምባቸው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page