የመብት ተሟጋች በሆኑ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ እየተጣለ ያለው እገዳ የሲቪክ ምህዳሩን እንዳያጠበው ስጋት ፈጥሯል ተባለ፡፡
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በተደጋጋሚ በመብት ተሟጋች የሲቪክ ማህበራት ላይ እየተጣለ ያለው እገዳ በመደራጀት መብት ላይም አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳያሳድር ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ሲል አሳስቧል፡፡
ኮሚሽኑ #የሲቪል_ማህበረሰብ_ድርጅቶች ባለስልጣን በህዳር ወር በተለያዩ 3 ድርጅቶች ላይ እገዳ ማስተላለፉን አቤቱታዎች ደርሰውኛል ብሏል፡፡
የሲቪል ድርጅቶች ከፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ መስራት ሲገባው ከአላማው ውጭ በመንቀሳቀስ የሃገርን ጥቅም የሚጎዳ ተግባር ላይ ተሰማርቷል በሚል የእገዳ ደብዳቤ እንደደረሳቸው አረጋግጫለሁ ብሏል ኢሰመኮ፡፡
እንዲሁም ባለፈው ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ተጨማሪ ሁለት በ #ሰብአዊ_መብት ዙሪያ የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፈፅመውታል የተባለው ከባድ የህግ ጥሰቶች በዝርዝር ባላስቀመጠ ደብዳቤ መታገዳቸውም አሳሳቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ ብሏል ኢሰመኮ፡፡
የመብቶች እና ዲሞክራሲ እድገት ማዕከል፣ የህግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች እና ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ የተባሉ 3 በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሰሩ ተቋማት መታገዳቸው ይታወሳል፡፡
ታህሳስ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ተቆጣጣሪ መ/ቤቱ በፃፈው ደብዳቤ እግዱን አንስቶ የነበረ ቢሆንም በ3 ቀን ውስጥ እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ #የእግድ_ደብዳቤ ደርሷቸዋል ተብሏል፡፡
እንዲሁም የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ሌላ 2 ተቋማትን ማገዱን ኢሰመኮ ባደረግሁት ክትትል አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡
በተጠቀሰው ቀን የታገዱትም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ናቸው፡፡
እንዲህ ያለው እገዳ የሲቪክ ምህዳሩን ከማጥበብ ባሻገር በማህበር የመደራጀት መብት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል ሲልም ኮሚሽኑ ጠቅሷል፡፡
በመሆኑም ተቆጣጣሪ መ/ቤቱ የድርጅቶችን የእለት ተዕለት እንቅስቃሴ ወደ ስራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ እንዲያመቻች ጥሪ አቅርቧል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q
📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Kommentare