top of page

ታህሳስ 18፣ 2015- በስፔን አንድ አውቶብስ ድልድይ ጥሶ ወንዝ ውስጥ በመውደቁ ሰባት ሰዎች መሞታቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Dec 27, 2022
  • 1 min read

በስፔን አንድ አውቶብስ ድልድይ ጥሶ ወንዝ ውስጥ በመውደቁ ሰባት ሰዎች መሞታቸው ተሰማ፡፡


አደጋው የደረሰው በሰሜናዊው ጋሊሲያ ግዛት እንደሆነ TVP ፅፏል፡፡


አውቶብሱ ድልድዩን ጥሶ የ30 ሜትር ያህል ጥልቀት ካለው ወንዝ ውስጥ መውደቁ ታውቋል፡፡


ባለስልጣናት አደጋው ምናልባትም በመጥፎ የአየር ሁኔታ ሳቢያ ሳይደርስ እንዳልቀረ ግምታቸውን ተናግረዋል፡፡


ብዙዎቹ መንገደኞች በሕይወት መትረፋቸው ታውቋል፡፡


አደጋው የገጠማቸው አብዛኞቹ የታሰሩ ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ ሲጓዙ የነበሩ ናቸው ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ

ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page